Skip to content
ውድድሮች
ውጤቶች
አባልነት
ስለ እኛ
Menu
ውድድሮች
ውጤቶች
አባልነት
ስለ እኛ
የኢትዮጵያ ወርቅ ደረጃ -ውድድር አዘገጃጀት
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለላቀ ደረጃ ለመድረስ ሁሌም የሚተጋ
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ኃላ.የተ.የግ.ማ. የሩጫ ውድድሮች በተለይም የጎዳና ላይ የብዙሃን ሩጫን በማዘጋጀት የሚታወቅ ድርጅት ነው፡፡ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከተጀመረ ጀምሮ ከ100 በላይ የሩጫ ውድድሮችን በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች አድርጓል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኩባንያው በሁሉም የኢትዮጵያ ማዕዘናት የብዙሃን ተሳትፎ ውድድሮችን በማካሄድ ላይ ትኩረት አድርጓል። ቋሚ ሰራተኞቹ እና አዘጋጅ ቡድኖቹ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን የተደራጀው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከተለያዩ አጋሮቹ ጋር በመሆን የውድድር እና ተያይዞም አጋሮቹን የማስተዋወቅ ዘመቻዎች ላይ በስፋት እየሰራ ይገኛል። ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በጋና የሚሊኒየም ማራቶን እና በደቡብ ሱዳን ጁባ ታላቁ የደቡብ ሱዳን ሩጫን ጨምሮ በተለያዩ የአፍሪካ ውድድሮች ላይ የምክር አገልግሎትም ሰጥቷል።
ራዕያችን፡ ሩጫን ለሁሉም ሰው የአኗኗር ዘይቤ ማድረግ!
ተልዕኳችን፡- ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የጅምላ ተሳትፎ ውድድሮችን በማዘጋጀት የኢትዮጵያን ገጽታ ማሳደግ፣ ጤናማ ኑሮ እና ጠቃሚ ማህበራዊ መልዕክቶችን ማስተዋወቅ እና ለወጣት አትሌቶች የመወዳደሪያ መድረክ በመፍጠር የአለም አቀፍ ውድድሮች ላይ የሚሳተፉበትን እድል ይፈጥራል።