እድሜያቸው ከ14 አመት በታች የሆኑ ልጆች ሩጫ ውድድር ለ14ተኛ ጊዜ ሚያዚያ 30 ቀን ይካሄዳል፡፡

Share This Post

Share on facebook
Share on linkedin
Share on twitter
Share on email

መጋቢት 26 ቀን 2014 ዓ.ም፡- የ2014 አውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ ውድድር ምዝገባ ዛሬ መጋቢት 26 ቀን ተጀምሯል፡፡

ህፃናት በሰውነታቸው የጎለበቱ እና ንቁ አዕምሮ ያላቸው እንዲሆኑ የተለያዩ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ማድረግ እንዳለባቸው ይመከራል፡፡ ለዚህም የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማድረግ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በአመት ሁለቴ ህዳር እና ሚያዚያ ላይ የህፃናት ሩጫን ላለፉት 13 አመታት አካሂዷል፡፡

በዚህ ውድድር ላይ ተሳታፊ የሚሆኑት ህፃናት ኢትዮጵያውያንና በሃገሪቱ ውስጥ የሚኖሩ የውጪ ማህበሰብ ልጆችንም የሚያካትት ሲሆን፤ በአራት የተለያዩ የእድሜ ክልሎች (ከ5፣ ከ8፣ ከ11 እና ከ14 በታች) በወንድና በሴት ተከፋፍሎ የሚካሄድ ይሆናል፡፡ ሩጫው ኢምፔሪያል ሆቴል አካባቢ በሚገኘው የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት ማዕከል የተለያዩ የህፃናት መዝናኛዎችን፤ ጌም ዞኖችን ጨምሮ ይካሄዳል ፡፡

እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ሜይ 9 ቀን ተከብሮ የሚውለውን የአውሮፓ ህብረት የተቋቋመበትን የሮም ስምምነትን በዓል ተያያዥ አድርጎ በየአመቱ የሚያደረገው የህፃናት ሩጫ እሁድ ሚያዚያ 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ለ14ተኛ ጊዜ ይካሄዳል፡፡ ውድድሩ 2000 ተሳታፊዎች ይኖሩታል፡፡

More To Explore

10KM

የ2015 ሌሎችን ለመርዳት እሮጣለሁ ዘመቻ የታቀደለትን ገቢ አሰባስቦ ለሶስት በጎ አድራጎት ድርጅቶች አስረከበ፡፡

በዘመቻው ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ በተለያዩ መንገዶች ተሰብስቧል፡፡ ታህሳስ 27 ቀን 2015 ዓ.ም.፡- ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ቢሮ ጋር በመተባበር የተለያዩ